Home Tech Talk አባይና የግድባችን ጉዳይ በቴክኖሎጂ እና ሳይንሳዊ እይታ ሲቃኝ – ቆይታ ከሃድሮሎጂስት እና የውሃ ሃብት መሃንዲስ ዶክተር ጥሩሰው አሰፋ ጋር – S17

አባይና የግድባችን ጉዳይ በቴክኖሎጂ እና ሳይንሳዊ እይታ ሲቃኝ – ቆይታ ከሃድሮሎጂስት እና የውሃ ሃብት መሃንዲስ ዶክተር ጥሩሰው አሰፋ ጋር – S17

by EthiopianSoftware

አባይና የግድባችን ጉዳይ በቴክኖሎጂ እና ሳይንሳዊ እይታ ሲቃኝ – ቆይታ ከሃድሮሎጂስት እና የውሃ ሃብት መሃንዲስ ዶክተር ጥሩሰው አሰፋ ጋር – S17



በሃገርም በውጪም ያለን ኢትዮጵያውያን ሁላ በአባይና የህዳሴው ግድብ ዙሪያ የማያወላዳ አቋም እና በአንድነት ሆነት የምንሞግትለት ብሄራዊ ጉዳይ ነው። የግድቡ ነገር ሲነሳ ከታችኛው ተፋሰስ አገራት በተለይም ከግብጽ ጋር በተያያዘ በብዛይ በዜናም ይሁን በማህበራዊ ሚዲያ የምናየው ፓለቲካዊ መልክ ያለውን ሙግት ነው። በዚህ ፕሮግራም ላይ ሳይንሳዊ እና ቴክኖሎጂያዊ ይዘቱን ለመነጋገር ከነዚህም ሳይንሳዊ እና ቴክኖሎጂያዊ ትንተና አንጻር ኢትዮጵያ 85 ከመቶ የውሃ መጠን እንደማበርከቷ አባይን ለሃይል ማመንጫነት የመጠቀም ተፈጥሮአዊ መብቷን የሚያረጋግጥ ውይይት ለማድረገ በሃይድሮሎጂ እና በውሃ ምንህድስና የተሰማራ ኢትዮጲያዊ ባለሞያ ጋብዣለሁ።

ዶ/ር ጥሩሰው አሰፋ በአሁን ሰዓት በፍሎሪዳ ግዛት በምትገኘው ታምፓ ቤይ ከተማ የውሃ ልማት ውስጥ በሃላፊነት ያገለግላል። በዚህ ሃላፊነቱ የተቋሙን ከ$200 to $400 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ሰፊ የፕሮጀክት ይቆጣጠራል።

ዶክተር ጥሩሰው የዶክትሬት ዲግሪውን ከUtah State University በCivil and Environmental Engineering ተቀብሏል። የማስተርስ ዲግሪውንም ከFree University of Brussels በሃይድሮሎጂ የተቀበለ ሲሆን የመጀምሪያ ዲግሪውንም በመስኖ ምህንድስና ከአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ተቀብሏል። ጭውውታችን እነሆ!

You may also like

Leave a Comment